ማክሰኞ 14 ኖቬምበር 2017

ሮበርት ሙጋቤ

በአወዛጋቢነት ከሚታወቁት ሮበርት ሙጋቤ ከበርካታ ቀልዶቻቸው መካከል ጥቂቶቹን እነሆ !!

ከሚስተር በርጫ ገጽ የተገኘ
:
1:- አፍሪካ ውስጥ በስነ-ስርዓት የሚከበረው ማስጠንቀቂያ "battery low !"የሚለው ብቻ ነው።
:
2:- ሴቶች በሙሉ የኤድስ መድሃኒት እስኪገኝ ድረስ የግብረ ስጋ ግንኙነት (Sex) አንፈጽምም ብለው ቢያምጹ ኖሮ፡ ወንዶች በ30 ቀናት ውስጥ መድሃኒቱን ባገኙት ነበር።
:
3:- ናይጄርያን የመሰሉ ብዙ ቋንቋዎች የሚናገር ህዝብ ያላቸው አገሮች፡ ዱዳ (መስማት የተሳነው) ፕሬዝደንት ነው የሚያስፈልጋቸው።
:
4:- አዳምና ሄዋን ቻይናዊያን ቢሆኑ ኖሮ፡ እስካሁን ድረስ ገነት ውስጥ በኖርን ነበር። ምክንያቱም የእጸ በለስ ፍሬውን ትተው እባቡን በበሉት ነበር።
:
5:- ከአንድ ሰው በላይ የምታፈቅር ከሆነ፡ ውስጥህ ያለው ልብ ሳይሆን'memory card' ነው፡
:
6:- አንዳንድ ጊዜ ወደ ኋላ መለስ ብለህ ስትመለከት ከእናትህ በላይ ለሴት ልጅ ገንዘብ የምታጠፋ ከሆነ ያኔ እጀ-ሰብ እውነት መሆኑ ይገባሃል።
:
7:- አንዳንድ ሴቶችን ስትመለከት ጂም የሚሰሩ ይመስላሉ። ግን የጂምናዝየምን በር እንኳ አይተውት አያውቁም። ሆኖም ግን ከአንዱ ወንድ ወደ ሌላው ወንድ ለመሮጥ ሲሉ ቅርጻቸውን ይጠብቃሉ።
:
8:- ትዳር እያለህ ከተማሪ ሴቶች ጋር መውጣት ደስ የሚልህ ከሆነ ለሚስትህ የተማሪ ዩኒፎርም ግዛላት፡፡
:
9:- ሰይጣን ራሱ gay አልነበረም፡ ምክንያቱም እራቁቱን ከነበረው አዳም እራቁቷን የነበረችውን ሄዋንን ስለመረጠ፡፡
:
10:- አስቀያሚ ከሆንክ አስቀያሚ ነህ ስለ ውስጣዊ ውበት አትናገር ምክንያቱም X-ray እያየን አይደለም የምንሄደው፡፡
:
11:- አምላክ ምርጥ ተመራማሪ ነው፡፡ ምክንያቱም ከወንድ ልጅ የጎድን አጥንት ወስዶ ድምጽ ማጉያ (loud speaker) ፈጠረ፡፡
:
12:- ዓለም አፍሪካን በድላታለች……
:
ከአውሮፓ አንድ ነጭ ወደ አፍሪካ ከመጣ የውጪ ዜጋ ጎብኚ ይባላል።
:
ከአፍሪካ አንድ አፍሪካዊ ወደ አውሮፓ ከሄደ ግን ህገ ወጥ ስደተኛ ይባላል፡፡
:
በግሩፕ ነጮች ወደ አፍሪካ ከመጡ ቱሪስት ይባላሉ፡፡ በብዛት አፍሪካዊያን ወደ አውሮፓ ከሄዱ ደግሞ ረፍዩጂስ (ስደተኞች) ይባለሉ።
:
ነጮች አፍሪካ ውስጥ መጥተው የአፍሪካዊያን አሰሪ ይሆናሉ፡፡ አፍሪካዊያን አውሮፓ ሄደውም የነጮች ሰራተኛ ነው የሚሆኑት……
:
:
ስለዚህ ዓለም በአፍሪካ ላይ ፍትሓዊት እንዳልሆነች በዚህ እንረዳለን፡፡
:
:

ዓርብ 6 ኦክቶበር 2017

ከማሥተዋል ማዶ

አምፖል ተቃጠለ ተብሎ ቤት
አይቀየርም!"
☞ አበቦች ሲፈኩ እንደሚደርቁ
ያውቃሉ ግን እደርቃለሁ ብለው
ሳይፈኩ አይቀሩም ፡፡ ሰውም
ሟች ነው ግን ሟች ነኝ ብሎ
ከመፍካትና ስኬታማ ለመሆን
ከመታተር መስነፍ የለበትም፡፡
ሁሉም ሰው በየመስኩ ያብብ
፡፡ ወዳጄ ይህቺ አለም ትልቅ
ደመራ ናት ።
☞ አንተ በደመራው ስር ያለህ
አንድ ችቦ ነህ አንተ ስትጠፋ
የደመራው ብርሀን ይቀንሳል ፡፡
የቻልከውን ያህል ብራ አንተ
ከነገሮች በላይ ነህ ፡፡ በነገሮች
አትረበሽ ፡፡ አየህ አምፖል
ተቃጠለ ተብሎ ቤት
አይቀየርም ፡፡ አምፖል
ተቃጥሏል ብሎ ቤት
የሚቀይር ሞኝ ነው ፡፡
አንተም አንዱ የህይወቴ ጉዳይ
አልተሳካም ብለህ ተስፋ
አትቁረጥ ራስህን አታጥፋ ፡፡
ይልቅስ አምፖልህን ቀይር
ችግርህን ተጋፈጠው ፡፡
ጭንቀትህን አስጨንቀው ፡፡
ካህሊል ጅብራል እንዲህ ይላል
ህይወት ልክ እንደ ክራር ጨዋታ
ነው ፡፡ አጨዋወቱን ያወቀ
ጥሩ ሙዚቃ ይሰማል ያላወቀ
ደግሞ ዝብርቅርቅ ጩኸቷን
ለመስማት ይገደዳል ፡፡
አሁንም እልሀለው ህይወት
በደመነፍስ አትሄድም ስልቷን
እወቀው ፡፡በህይወትህ ትላንት
ያለፈውን መጥፎ ህይወትህን
መቀየር ማስተካከል መሰረዝ
አትችልም ፡፡ የምትችለው
አምኖ መቀበልና ለተሻለ ነገ
መስራት ነው ፡፡
☞ "መቀየር የማንችለውን ነገር
መቀበል ማለት ተስፋ
መቁረጥ ማለት ሳይሆን
አቅማችንን የምንችለው ነገር
ላይ ማዋል ማለት ነው ::"
በፍፁም ተስፋ አትቁረጥ ግን
አቅምህን የምትችለው ነገር
ላይ አውለው ። ደግሞም አንድ
ነገር አስታውስ "በሚያልፍ ቀን
ውስጥ የማያልፈውን
አምላክህን ተመልከት ።

ሠብልዬ