እሑድ 27 ዲሴምበር 2015

አድዋ
የሰው ልጅ ክቡር ሰው መሆን ክቡር
ሰው ሞቷል ሰው ሊያድን ሰውን ሊያከበር::
በደግነት በፍቅር በክብር ተጠርቶ በክብር ይሄዳል
ሰው ሊኖር ሰው ሞቷል፡፡
የተሰጠኝ ህይወት ዛሬ በነጻነት
ሰው ተከፍሎበታል ከደም እና ከአጥንት
ስንት ወገን ወደቀ በነጻነት ምድር
ትናገር አድዋ ትናገር ትመስክር፡፡
ትናገር አድዋ ትናገር ሃገሬ
እንዴት እንደቆምኩኝ ከፊታችሁ ዛሬ፡፡
በኩራት በክብር
በደስታ በፍቅር
በድል እኖራለው ይኀው በቀን በቀን
ደግሞ መከራውን ያን ሁሉ ሰቀቀን
አድዋ ዛሬ ናት አድዋ ትላንት
መቼ ተነሱና የወዳደቁት፡፡
ምስጋና ለነሱ ለአድዋ ጀግኖች
ለዛሬ ነጻነት ላበቁኝ ወገኖች፡፡
የጥቁር ድል አምባ አድዋ
አፍሪካ እምዬ ኢትዮጵያ…!!!
አዎ ተናገሪ ተናገሪ
የድል ታክሽን አውሪ፡፡
በእጅጋየው ሽባባው

ቅጠል እየበጠስሽ ስትጥይ አይቻለሁ

በአንድ ወቅት ባልና ሚስት የጦፈ ጭቅጭቅ ውስ
ናቸው የጭቅጭቃቸው መንስኤ ደግሞ የባል ደከማና ማየት
የተሳናቸው እናት ነበሩ ታዳ ሚስቲቱ የባሏን እናት ቤት ውስጥ
አስቀምጦ መጦሩን አልወደደችም ነበር:: በዚህ የተነሳው
መቇጫ ያላገኘውን
ጭቅጭቅ እኔን ወይም እናትህን ምረጥ በሚለው በሚስት
ተብየዋ የመጨረሻ ንግግር ረገብ አለ!...... ባልም አውጥቶ
አውርዶ,,,, ቇጥሮ ከፈታ ቡሃላ ሚስቱን መረጠ እናም ከሚስቱ
ጋር ተመካክሮ ራቅ ብሎ ከሚገኘው ጫካ ውስጥ እናቱን
ለመጣል ወሰነ.... ወስኖም አልቀረ እናቱን አዝሎ ወስዶ ጫካ
ውስጥ ጥሏቸው ተመለሰ:: ታዳ በዚህ
ጊዜ እውነታውን ሲከታተል የነበረ አንድ ሽፍታ ወደ እናትየዋ
ተጠግቶ እንዲህ አላቸው <<ልጅሽ እዚህ አስፈሪ ጫካ
ውስጥ
ጥሎሽ ተመለሰ ነገር ግን አዝሎ ሲያመጣሽ ጀርባው ላይ
ሆነሽ
ቅጠል እየበጠስሽ
ስትጥይ አይቻለሁ
ለምንድን ነበር እንደዛ ያደረግሺው>> ብሎ ሲጠይቅ እናትም
እነዲህ አሉት <<ልጄ እኔን ጥሎኝ ሲመለስ መንገዱ ጠፍቶት
አውሬ እንዳይበላብኝ ምልክት እንዲሆነው ነው>> ብለው
መለሱለት..... እናት ለዘላለም ትኑር

ሞባይል አጠቃቀማችን እየገደለን ነው
• በተለይ ለወንዶች ሞባይሉን በፊት ለፊት የሱሪ ኪስ ውስጥ ወይም በብልታቸው በሚቀርብ ሁኔታ አይያዙ፡፡ ጨረሩ ሲደጋገም ለመሀንነት ያጋልጣል፡፡
• ሞባይሎን ኪስዎ ውስጥ የሚያደርጉ ከሆነ ወይም በወገብ የሚታጠቁት ከሆነ ኪፖድ ወይም የቁጥር ቁልፎችን ወደ ሰውነትዎ አቅጣጫ ያድርጉ፣ ማለትም የስፒከሩ ፊት ወደ ውጭ ይሁን፣ ምክንያቱም ስልክ ሲደወል ጨረሩ በስፒከሩ በኩል ስለሚለቀቅ ወደ ሰውነትዎ ሳይሆን ወደ አየሩ ይበተናል፡፡ ወደ ሰውነት የመግባት እድሉ አነስተኛ ነው፡፡ ጠረጴዛ፣ አልጋ፣ ወንበር….ወዘተ ላይ ሲያስቀምጡትም ስፒከሩ ወደ መሬት አቅጣጫ፣ ቁጥሩ ደግሞ ወደ ላይ ይሁን፡፡
• ሞባይል ተጠቃሚ ከሆኑ ሲነጋገሩ ወደጆሮዎ እና ጭንቅላትዎ እጅግ በጣም አያስጠጉ፡፡ ቢያንስ ከ5 ሳንቲ ሜትር በላይ ራቅ ማድረግ ኤሌክትሮማግኔቲክ ራዲየሽን ከተባለው አደገኛ ጨረር ራስዎን ይጠብቃሉ፡፡
• ሞባይሎን ታቅፈው አይተኙ፡፡ በእንቅልፍ ወቅት ባትሪውን ያጥፉ ወይም ከአልጋዎ 1.8 ሜትር ያርቁት፡፡ ማታ ሲደወል ከሚለቀቀው ኤሌክትሮማግኔትክ ራስዎን በተቻለ መጠን አያጋልጡ፡፡
• ነፍሰጡር እናቶች ሞባይል ሲይዙና ሲጠቀሙ ይጠንቀቁ፡፡ የጽንሱ ሕዋሳት ለኤሌክትሮማግኔቲክ ራድየሽን እጅግ በጣም አለርጂክ ናቸው፡፡ ስለዚህ አቀማመጡንም ሆነ አጠቃቀሙን ከጽንሱ ራቅ ባለ ሥፍራ ይሁን፡፡ አላስፈላጊ አጠቃቀምን ለምሳሌ ረጅም ሰዓት ማውራት እና ቶሎ ቆሎ መደዋወል መቀነስ አለበት፡፡
• ብረት ነክ ነገሮች ባሉበት ሥፍራ ሞባይል አይጠቀሙ፡፡ ብረት የኤሌክትሮማግኔቲክ ራድየሽኑን ወይም የጨረሩን ጉልበት ያጠነክረዋል፡፡ ስለዚህ መኪና ውስጥ፣ አውሮፕላን ውስጥ፣ ሊፍት ውስጥ፣ ባቡር ውስጥ፣ ብረት አጥር ወይም በር አካባቢ፣ የብረታብረት ወርክሾፕ ውስጥ፣ ጋራዥ ውስጥ ወዘተ አስቸኳይ ወይም አጣዳፊ ጉዳይ ካልሆነ በስተቀር በተቻለ መጠን ሞባይል አይጠቀሙ፡፡ የሚጠቀሙም ከሆነ በአጭር ደቂቃ ብቻ ይሁን፡፡
• በተለይ! በተለይ!!! ዕድሜያቸው ከ15 ዓመት በታች የሆኑ ወጣት ልጆች ሞባይልን ባይጠቀሙ ወይም ባያዘወትሩ ይሻላል፡፡ ጨረሩ የጭንቅላት ሴሎቻቸውን እጅግ በጣም ይጎዳዋል፤ ለካንሰርም ያጋልጣቸዋል፡፡
• በበለጸጉት አገሮች ከ15 ዓመት በታች ባሉ ልጆች ውስጥ ለሚከሰተው ሞት በሁለተኛ ደረጃ የተቀመጠው ምክንያት የጭንቅላት እጢ ነው፡፡ ወላጆች ይህንን እውነታ በመገንዘብ አልፎ አልፎ ካልሆነ በስተቀር ሞባይል መጠቀምን በመደበኛነት ልጆች አዘውትረው እንዳይለምዱት ማድረግ ይገባቸዋል፡፡
• አዲስ የተወለዱ ጨቅላ ሕፃናት ዕድሜያቸው ከ2 ዓመት በታች የሆኑት ሁሉ የጭንቅላታቸው ራስ ቅል በጣም ስስ ነው፡፡ ስለዚህ ጨረሩ ሙሉ ለሙሉ በስሱ አጥንት በኩል ወደ አንጎላቸው ይሰርፃል፡፡
• ጨቅላ ሕፃናትና ትናንሽ ልጆች አጠገብ ሁነው ሞባይል አዘውትረው የሚነጋገሩ ከሆነ ለአደጋ ስለሚያጋልጣቸው አጠቃቀሙንና አቀማመጡ ከእነርሱ ራቅ ባለ ሁኔታ ላይ ያድርጉት፡፡
• የባትሪ ቻርጅ በጣም ሎው ሲሆን፣ ወይም ሲቀንስ ስልኩን ያለመጠቀም ልማድ ይኑርዎ፡፡ ምክንያቱም ቻርጅ ሲቀንስ የሚረጨው የጨረር መጠን ይጨምራል!
-‹‹የዕውቀት ማኅደር›› (2005)

ማክሰኞ 22 ዲሴምበር 2015

በበዕዉቀቱ ሥዩም
ትናንትና ማታ
ላሟሟሽ ሲገባኝ፣እንዳሞሌ አጥቤሽ
በመጨረስ ፋንታ
ለነገ ቆጥቤሽ
አስተርፌሽ ለሰው
የጸጸት ሱናሚ ፤ዓለሜን አመሰው፡፡
ምነው ቢቻል ኖሮ
ፈገግታሽን ቋጥሮ
ሙዳይ ውስጥ መደበቅ
ጃንደረባ ቀጥሮ
ጭንሽን ማስጠበቅ
ክፍት ልቤን ይዤ፤ ዝግ ደጅሽን ጠናሁ
በሰበብ ወድጄሽ ፤ያለሰበብ ቀናሁ፡፡
ፍቅር በተባለ፤ ግራ- ገቢ ነገር
ከጨመተው አገር
ከሰከነው ቀየ
መናፍቅ ይመስል፤ ባዋጅ ተነጥየ
እንደካፖርቴ ቁልፍ፤ ልቤን የትም ጥየ
የትም ስከተልሽ
የትም ሆኖ እድልሽ፤
ሁሉ ያንች ወዳጅ
ሁሉ ባላንጣየ
መፈቀር ሆኖ ጣሽ፤ መቅናት ሆኖ ጣየ
ላንቺ ብስል ፍሬ፤ ለኔ ገለባ ግርድ
ላንቺ እቅፍ አበባ፤ ለኔ እቅፍ ሙሉ ብርድ
ማነው የበየነው ፣ይህን ግፈኛ ፍርድ፡
በበዕዉቀቱ ሥዩም